1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ሴቶችን ወደውሳኔ ሰጭነት የማሳደግ ዕድል እና ተግዳሮት

ሰኞ፣ ነሐሴ 13 2011

ሴቶችን  ወደ ውሳኔ  ሰጭነት  ለማምጣት  በፌደራል  ደረጃ  የታዩ  ጅምሮች  ቢኖርም  በታችኛው የአስተዳደር  መዋቅሮች  ግን  አሁንም  ሰፊ  ክፍተት  እንደሚስተዋል ተጠቆመ ።

https://p.dw.com/p/3O8nM
Äthiopien Podiumsdiskussion Challenges and opportunities for women empowerment
ምስል DW/S. Wegazehu

ሴቶችን ወደውሳኔ ሰጭነት የማሳደግ ዕድል እና ተግዳሮት

 የሀዋሳ  ዩኒቨርሲቲ ሴቶችን  ወደ ውሳኔ  ሰጭነት  ለማምጣት  በሚያጋጥሙ  ተግዳሮቶች እና ዕደሎች ላይ የሚመክር የፓናል ውይይት ዛሬ  በሀዋሳ  ከተማ  አካሂዷል። በፓናል  ውይይቱ  ላይ  ሴቶች  እራሳቸውን ለማብቃት  በሚያደርጉት  ጥረት  ከሚያጋጥሞቸው  ችግሮች  መካከል  የፆታ  ትንኮሳ እና ጥቃት በዋነኝነት  እንደሚጠቀስ  ተገልጿል ። የሴቶችን መብት የሚመለከቱ ጉዳዮችን ከመረዳት አኳያ በአካዳሚው የትምህረት ሂደት የትኛውም ደረጃ ላይ መገኘት በቂ ግንዛቤ ለመኖሩ ማሳያ እንደማይሆንም ተጠቅሷል። የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ዛሬ በሀዋሳ ከተማ ባዘጋጀው የፓናል ውይይት / ሴቶችን ወደ ውሳኔ ሰጭነት ለማምጣት በሚያጋጥሙ ተግዳሮቶች እና  ዕድሎች ላይ የተለያዩ  ሃሳቦች ተነስተው ውይይት ተደርጎባቸዋል ። ውይይቱን  የተከታተለው  የሀዋሳው  ወኪላችን  ሸዋንግዛው ወጋየሁ ተከታዩን  ዘገባ  ልኮልናል።

ሸዋንግዛው ወጋየሁ

ሸዋዬ ለገሠ

አዜብ ታደሰ