1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ሲዳማ ክልል፣ 12 ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት መሰረቱ

ሐሙስ፣ መጋቢት 2 2013

በመጪው አገራዊ ምርጫ ለመወዳደር በሲዳማ የምርጫ ክልሎች የሚንቀሳቀሱ 12 ፓርቲዎች «በምርጫ ሂደት ሊነሱ የሚችሉ ቅሬታዎችና አለመግባባቶችን በውይይት ለመፍታት ያስችለናል» ያሉትን የጋራ ምክር ቤት መሰረቱ።

https://p.dw.com/p/3qVB1
Äthiopien Die politischen Parteien gründen einen Versammlungsrat - Hawassa
ምስል Shewangizaw Wegayehu/DW

የስነ ምግባር ደንቦችና የቃል ኪዳን ሰነዶችንም ተፈራርመዋል

በመጪው አገራዊ ምርጫ ለመወዳደር በሲዳማ የምርጫ ክልሎች የሚንቀሳቀሱ 12 ፓርቲዎች «በምርጫ ሂደት ሊነሱ የሚችሉ ቅሬታዎችና አለመግባባቶችን በውይይት ለመፍታት ያስችለናል» ያሉትን የጋራ ምክር ቤት መሰረቱ። ፓርቲዎቹ የአገሪቱን ሕግ ለማክበርና ሰላማዊ የምርጫ ፉክክር ለማድረግ አጋዥ የሆኑ የስነ ምግባር ደንቦችና የቃል ኪዳን ሰነዶችንም ተፈራርመዋል። የጋራ ምክር ቤቱን መቋቋም ያወደሱት የኢትዮጲያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የስራ ሃላፊዎች በበኩላቸው የምክር ቤቱ መመስረት አንድም ተፎካካሪ ፓርቲዎችን ያቀራርባል፣ ሁለትም በምርጫ አፈጻጸም የሚጋጥሙ ችግሮችን በምክክር ለመፍታት ያስችላል ብለዋል።  

ሸዋንግዛዉ ወጋየሁ
ማንተጋፍቶት ስለሺ
አዜብ ታደሰ