ሰላማዊ የፖለቲካ ትግልና ትጥቅ በኢትዮጵያ
እሑድ፣ ጥቅምት 11 2011ማስታወቂያ
መንግሥት ባለፈው ሳምንት በይፋ ነፍጥ አንግቦ በተቃዉሞ ይንቀሳቀስ የነበረው እና በቅርቡ ወደሰላማዊ ትግል መግባቱ የተነገረለት የኦሮሞ ነፃ አውጭ ግንባር በምህጻሩ ኦነግ፤ አባላቱን ትጥቅ እንዲያስፈታ ፤ ያን ካላደረገ ደግሞ መንግሥት ራሱ ይህን ተግባራዊ እንደሚያደርግ አሳስቧል። የኦነግ መሪዎች ለዚህ የሰጡት ምላሽ ማነጋገር ይዟል። በሌላ በኩል ኢትዮጵያ በምትገኝበት የዚህ የሽግግር ወቅት የታጠቁ ቡድኖች ያደርሳሉ ከሚባለው ችግር ባልተናነሰ በኅብረተሰቡ ውስጥም የሚገኘው የጦር መሣሪያ ጥንቃቄ ሊደረግበት እንደሚገባ ምሁራን ይመክራሉ። የዶይቼ ቬለ የዚህ ሳምንት እንወያይ መሰናዶ የትጥቅ ፍቱ አንፈታም አካሄድ ወዴት ያመራል? በዛሬዋ ኢትዮጵያ በሰላማዊ መንገድ የፖለቲካ ሃሳብን ማራመድ እና የጠመንጃ እና ኃይል ፖለቲካስ እንዴት ይታያል? በሚሉት ላይ ምሁራንን አወያይቷል።
ሸዋዬ ለገሠ
ማንትጋፍቶት ስለሺ