1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

«ረሃብ የሀገሪቱ ስጋት አይደለም»

ረቡዕ፣ ታኅሣሥ 14 2013

የኮሮና ወረርሽኝ የፈጠረው የኢኮኖሚ መቀዛቀዝን በተጨማሪ ምክንያትነት የጠቀሰው ይሄው ድርጅት መንግሥት ሁሉን አቀፍ ድጋፍ እንዲያደርግ ጠይቋል። የብሔራዊ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን በበኩሉ የሰብዓዊ እርዳታ ፈላጊዎች እና የዕለት ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው ዜጎች ቁጥር ሊጨምር እንደሚችል ቢገመትም ረሀብ ግን የሀገሪቱ ሥጋት ሊሆን እንደማይችል ተናግሯል።

https://p.dw.com/p/3nAYu
Äthiopien Adama | Welt ohne Hunger | Traditionelle Weizenernte
ምስል Stefan Trappe/Imago Images

«ረሃብ የሀገሪቱ ስጋት አይደለም»

«ኢንተርናሽናል ረስኪዩ ኮሚቴ » የተባለ ግብረ ሰናይ ድርጅትት በኢትዮጵያ ውስጥ የተከሰተው የአንበጣ መንጋ እና የትግራይ ክልል ቀውስ በርካታ ዜጎችን ለረሀብና ለአስቸኳይ ርዳታ ፈላጊነት ሊዳርጋቸው ይችላል ሲል አሳሰበ። የኮሮና ወረርሽኝ የፈጠረው የኢኮኖሚ መቀዛቀዝንም ለዚህ ማስጠንቀቂያው በተጨማሪ ምክንያትነት የጠቀሰው ይሄው ድርጅት መንግሥት ሁሉን አቀፍ ድጋፍ እንዲያደርግ ጠይቋል። የብሔራዊ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን በበኩሉ የሰብዓዊ እርዳታ ፈላጊዎች እና የዕለት ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው ዜጎች ቁጥር ሊጨምር እንደሚችል ቢገመትም ረሀብ ግን የሀገሪቱ ሥጋት ሊሆን እንደማይችል ተናግራል። ሰሎሞን ሙጬ ከአዲስ አበባ ዝርዝሩን ልኮልናል።
ሰሎሞን ሙጬ
ኂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ