1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ሦስት የፖለቲካ ፓርቲዎች ሊዋሐዱ ነው

ሐሙስ፣ ታኅሣሥ 18 2011

ሦስት የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች ለውሕደት ዝግጅት ላይ ነን እያሉ ነው። ተዋሕደን ጠንካራ ፓርቲ ለመመስረት ተቃርበናል ያሉት ሰማያዊ ፓርቲ፣ የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ)፤  አርበኞች ግንቦት ሰባት ንቅናቄ ናቸው።

https://p.dw.com/p/3AhMz
Äthiopien vor der Wahl Blaue Partei Anhänger in Addis Abeba
ምስል Reuters/Tiksa Negeri

የዜግነት ፖለቲካ የማቀንቀን ውጥን አላቸው

ሦስት የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች ለውሕደት ዝግጅት ላይ ነን እያሉ ነው። ተዋሕደን ጠንካራ ፓርቲ ለመመስረት ተቃርበናል ያሉት ሰማያዊ ፓርቲ፣ የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ)፤  አርበኞች ግንቦት ሰባት ንቅናቄ ናቸው። የፖለቲካ አራማጆች፡ ከእስር የተፈቱ ሰዎችና ከውጭ የተመለሱ ታዋቂ ኢትዮጵያዊያን አዲስ ይመሰረታል ተብሎ በሚጠበቀው ፓርቲ ውስጥ ይሳተፋሉ ተብሏል። የሚመሰረተው የፖለቲካ ፓርቲ የኢትዮጵያዊያንን የጋራ እሴቶች ፡ ተስፋዎች እና ማህበራዊ ፍትህን የሚያቀነቅን እንደሆነ ታውቋል፡፡በውሕደቱ በመሰረታዊነት ስምምነት ላይ የተደረሰ ሲሆን የሚዋሃዱት ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤዎች በተናጠል  ሲያጸድቁት ህግንና አሰራርን ተከትሎ ይፈጸማል። ሰለሞን ሙጬ ተጨማሪ ዘገባ አለው
ሰለሞን ሙጬ

እሸቴ በቀለ
ነጋሽ መሐመድ