1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ምዕራብ ወለጋ አዲስ ግጭት

ማክሰኞ፣ ጥቅምት 23 2014

ዉጊያዉን ሸሽተዉ በኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የገቡ ተፈናቃዮች እንደሚሉት በግጭቱ ቁጥሩን በትክክል የማያዉቁት የአካባቢዉ ነዋሪ ተገድሏል። ከ3ሺሕ የሚበልጥ ሕዝብ ተፈናቅሏል፣ የስልክና የኢንተርኔት አገልግሎትም የለም።

https://p.dw.com/p/42U6G
Äthiopien Assosa | Schild des Krisenmanagement Büro für Benishangul Gumuz
ምስል DW/N. Dessalegn

የምዕራብ ወለጋ ግጭትን የሸሹ ተፈናቃዮች

በምዕራብ ወለጋ  ዞን ቤጊና ቆንዳላ በተባሉ ወረዳዎች  በሸመቁ ታጣቂዎችና  በኢትዮጵያ መከላከያ ጦር መካከል ባለፈዉ ቅዳሜ በተደረገ ግጭት በርካታ ሰዎች መገደላቸዉንና በሺሕ የሚቆጠሩ መፈናቀላቸዉን የአካባቢዉ ነዋሪዎች አስታወቁ። ዉጊያዉን ሸሽተዉ በኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የገቡ ተፈናቃዮች እንደሚሉት በግጭቱ ቁጥሩን በትክክል የማያዉቁት የአካባቢዉ ነዋሪ ተገድሏል። ከ3ሺሕ የሚበልጥ ሕዝብ ተፈናቅሏል፣ የስልክና የኢንተርኔት አገልግሎትም የለም። የበኒሻንጉል ጉሙዝ የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽንም ከሁለቱ ወረዳዎች የሸሹ ከ3ሺሕ በላይ ተፈናቃዮች መመዝገቡን አረጋግጧል።

ነጋሳ ደሳለኝ 

ነጋሽ መሐመድ

ማንተጋፍቶት ስለሺ