1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ምርጫ በደብረ-ብርሃን

ሰኞ፣ ሰኔ 14 2013

በደብረ ብርሃን የምርጫ ክልል የተመዘገቡ ከ73 ሺሕ በላይ ድምፅ ሰጪዎች የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የክልል ምክር ቤት ተወካዮቻቸውን ሲመርጡ ውለዋል። በከተማዋ የሚገኘው የዶይቼ ቬለ ዘጋቢ ያነጋገራቸው መራጮች የሚመረጠው መንግሥት ሊሠራ ይገባል የሚሏቸው በርካታ ጉዳዮች አሉ። ሰላምና ጸጥታ በበርካቶች ተደጋግመው ከሚነሱ ጉዳዮች አንዱ ነው።   

https://p.dw.com/p/3vHNR
Parlamentswahl in Äthiopien 2021
ምስል E. Bekele/DW

ከ73 ሺሕ በላይ ድምፅ ሰጪዎች ተመዝግበዋል

በደብረ ብርሃን የምርጫ ክልል የተመዘገቡ ከ73 ሺሕ በላይ ድምፅ ሰጪዎች የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የክልል ምክር ቤት ተወካዮቻቸውን ሲመርጡ ውለዋል። በከተማዋ የሚገኘው የዶይቼ ቬለ ዘጋቢ ያነጋገራቸው መራጮች የሚመረጠው መንግሥት ሊሠራ ይገባል የሚሏቸው በርካታ ጉዳዮች አሉ። ሰላም እና ጸጥታ በበርካቶች ተደጋግመው ከሚነሱ ጉዳዮች አንዱ ነው።   
በደብረ ብርሃ ከተማ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫዎች ብልፅግና ፓርቲ፣ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ-ፍትህ ፓርቲ፣ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ፣ እናት ፓርቲ፣ ኅብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ እና የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት ስድስት እጩዎች አቅርበዋል። ከስድስቱ አንዷ ብቻ እንስት ናቸው። ለአማራ ክልል ምክር ቤት ደግሞ ከኅብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ በቀር አምስቱ ፓርቲዎች ሁለት ሁለት እጩዎች ከተማዋን ለሚወክሉ መቀመጫዎች ያወዳድራሉ።

እሸቴ በቀለ

ማንተጋፍቶት ስለሺ

ሸዋዬ ለገሰ

ኂሩት መለሰ