መፍትሄ የሚሻው የሰላም ጉዳይ
እሑድ፣ ኅዳር 30 2011ማስታወቂያ
መንግሥት በበኩሉ ሰላምን የሚያውኩ የተደራጁ ኃይሎች መኖራቸውን በመጥቀስ የግጭቱ ለኳሾች ናቸው ያላቸውን ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር ማድረግ መጀመሩን ይገልጻል። የሰላም መደፍረስ ያሰጋቸው ዜጎች የሰላም ጥሪን ከክልል ክልል እየተዘዋወሩ እያቀርባሉ። ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉ ወገኖች ራሱ ገዢው ፓርቲ በውስጡ የተፈጠረው መቃቃር፤ የሕገወጥ የጦር መሣሪያ ዝውውር እና ለውጡ ያልተመቻቸው ኃይሎችን በምክንያትነት ያነሳሉ። የሰላም እና ብሔራዊ እርቅ አስፈላጊነት በሚነገርባት ሀገር እውነተኛ ሰላም ለማውረድ ለምን ጊዜ ወሰደ? የሚሉ ነጥቦችን በማንሳት የተካሄደውን ውይይት ከድምጽ ቅንብሩ ያድምጡ።
ሸዋዬ ለገሠ