1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

መረጋጋት የታየባት ጎንደር

ሰኞ፣ ጥቅምት 10 2012

ጎንደር ከተማ እና አካባቢው አንፃራዊ መረጋጋት እየታየበት እንደሆነ የከተማዋ ነዋሪዎች አመለከቱ። በሰሞኑ ግጭት ተርጥረው ከነበሩት መካከል 58ቱ ጉዳያቸው ተጣርቶ መለቀቃቸውን የጎንደር ከተማ አስተዳደር አስታውቋል።

https://p.dw.com/p/3RfMJ
Äthiopien Gondar
ምስል DW/A. Mekonnen

«በግጭቱ ተጠርጥረው ከተያዙ 58ቱ ተለቅቀዋል»

 የከተማው የሰላምና የሕዝብ ደህንነት መምሪያ ኃላፊ  አቶ ተስፋ መኮንን  ዛሬ ጎንደር ከተማ ውስጥ  ለዶይቼ ቬለ አንደገለፁት ሰሞኑን በጎንደርና አካባቢው ተፈጥሮ በነበረው ግጭት ምክንያት ተጠርጥረው በሕግ ጥላ ስር ከቆዩት 119 ተጠርታሪዎች መካከል  ጉዳቸው ተጣርቶ 58ቱ ተለቅቀዋል። ኃፊው እንዳሉት መንግሥት በአካባቢው ሰላም ለማረጋገጥ ያወጣውን መግለጫ ተከትሎ በከተማው የንግድ እንቅስቃሴና አጠቃላይ ሰላሙ እየተመለሰ ነዋሪውም መደበኛ ሥራውን በመስራት ላይ አንደሆነ አመልክተዋል። ኅብረተሰቡ መንግሥት ያወጣውን መግለጫ እንደተቀበለው አመልክተው መዘግት አልነበረበትም የሚል ቅሬታ ግን አንደነበረው አስረድተዋል።  

Äthiopien Gondar
ምስል DW/A. Mekonnen

ከጎንደር ከተማ ነዋሪዎች መካከል መምህር ዘላለም አዲስም መግለጫው መዘግት እንዳልነበረበት አመልክተው ቢሆንም አሁን ለተገኘው ሰላም አስተዋጽኦ አለው ነው ያሉት። በሰው ሕይወት ላይ ጉዳት መድረሱንና ሰዎች መፈናቀላቸውን የተተናገሩት አቶ ተስፋ የሟቾችንም ሆነ የተፈናቃዮችን ቁጥር አልገለፁም፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ በከተማው አንጻራዊ ሰላም መኖሩንና ወጣቶችም ሰላሙን ለማስቀተል እየሠሩ መሁኑን የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች አመልክተዋል። አስተያታቸውን ከሰጡኝ ነዋሪዎች መካከል አንዱ አቶ እንዳለው ፈቃዴ አንዱ ናቸው። ወጣቱ ቀን እና ሌሊት እየሠራ ነው።  አልፎ አልፎ የተኩስ ድምጽ ቢሰማም አሁን የተሻለ ነገር አንዳለ የገለፁት ደግሞ አቶ መሳፍንት ወርቁ ናቸው። ሌላው ነዋሪ አቶ ጌቱ ወርቁ አንደሚሉት የተገኘውን ሰላም ለማስቀጠል ወጣቱ ከጸጥታ ኃይሉ ጋር መሥራት ይገባዋል። ወደ ጎንደር የተጓዘው የባሕር ዳሩ ዘጋቢያችን በላከው ዘገባ ጠቅሷል።

ዓለምነው መኮንን

ሸዋዬ ለገሠ

ተስፋለም ወልደየስ