ሕወሓት ከሰሞኑ ከፍተኛ ጥቃት ሰንዝሯል፤ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች አገልግሎት
ቅዳሜ፣ ጥቅምት 20 2014ማስታወቂያ
ሕወሓት ባሰማረው ከፍተኛ "የመንጋ" ያሉት ወራሪ ኃይል ከሰሞኑ ከፍተኛ ጥቃት መሠንዘሩን የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች አገልግሎት ሚንስትሩ ለገሰ ቱሉ ተናገሩ። ከመደበኛ የጦርነት ባሕሪ የወጣውን ጥቃት ለመመከት ሁሉም ኢትዮጵያዊ ርብርብ እንዲያደርግ ጥሪ መቅረቡንም ገልጸዋል። "የወገን ጦር ውስጥ ተቆርቋሪ በመምሰል ባንዳ ሆነው የሚያገለግሉ ኃይሎች አሉ" ያሉት ሚንስትሩ የመከላከያ ኃይል እና የፀጥታ ኃይሎች ሥራዎቻቸውን ለመሥራት ሲንቀሳቀሱ ባንዳ ባሏቸው አካላት የማወክ ፣የማገድ፣ እንቅፋት የመሆን ሁኔታ መኖራቸውን ገልፀዋል። ሚንስትሩ ዛሬ ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫ ሰጥተዋል። ሰለሞን ሙጬ መግለጫውን ተከታትሎታል።
ሰለሞን ሙጬ
ታምራት ዲንሳ