1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ሊቢያ የሰፈሩ ስደተኞች መገደል

ሐሙስ፣ ሰኔ 27 2011

ግብፅ፣ሳዑዲ አረቢያ፤የተባበሩት አረብ አሚራት እና ፈረንሳይ ይደግፏቸዋል የሚባሉት የጦር አበጋዝ ኻሊፋ ሐፍጣር የጦር ጄቶች እንደጣሉትን በሚታመነዉ ቦምብ 44 ስደተኞች ተገድለዋል።ከ130 በላይ ቆስለዋል

https://p.dw.com/p/3LaX3
Libyen Tripolis nach dem Luftangriff auf das Tajoura Detention Center
ምስል Getty Images/AFP/M. Turkia

የስደተኞች መገደልና የዓለም ደንታቢስነት

                           

 

ሊቢያ ርዕሠ ከተማ ትሪፖሊ አጠገብ በሚገኘዉ ታጁራ መጠለያ ጣቢያ የተጠለሉ ስደተኞች ትናንት በጦር ጄት ተደብብድበዉ መገደላቸዉን የተለያዩ የስደተኞች መብት ተሟጋች ድርጅቶች ማዉገዛቸዉን እንደቀጠሉ ነዉ።ትናንት በጉዳዩ ላይ ለመነጋገር ተሰይሞ የነበረዉ የተባበሩት መንግሥታት የፀጥታዉ ምክር ቤትም ሆነ፣ መንግሥታት ግን እስካሁን ግድያዉን  አላወገዙም።ግብፅ፣ሳዑዲ አረቢያ፤የተባበሩት አረብ አሚራት እና ፈረንሳይ ይደግፏቸዋል የሚባሉት የጦር አበጋዝ ኻሊፋ ሐፍጣር የጦር ጄቶች እንደጣሉትን በሚታመነዉ ቦምብ 44 ስደተኞች ተገድለዋል።ከ130 በላይ ቆስለዋል።

 ገበያዉ ንጉሴ 

ነጋሽ መሐመድ

ኂሩት መለሰ