1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

«CPJ» የድሪደዋ ጋዜጠኞች ጥቃት እንዲመረመር ተጠየቀ

ማክሰኞ፣ ሐምሌ 17 2010

በድሬዳዋ መገናኛ ብዙኃን የጋዜጠኞች ቡድን ላይ የተፈፈፀዉን ጥቃት መንግስት እንዲያጣራ ለጋዜጠኞች መብት የሚሟገተዉ ድርጅት «CPJ» ጠየቀ። ጋዜጠኞቹ ጥቃት የደረሰባቸዉ የፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂን ወደ ኢትዮጵያ መምጣት ለመዘገብ ከድሬደዋ ወደ መዲና አዲስ አበባ ሲጓዙ ነዉ። በጥቃቱ አንድ ሰዉ ሞቶአል።

https://p.dw.com/p/321e0
Logo CPJ
ምስል APTN

በድሬዳዋ መገናኛ ብዙኃን የጋዜጠኞች ቡድን ላይ የተፈፈፀዉን ጥቃት መንግስት እንዲያጣራ ለጋዜጠኞች መብት የሚሟገተዉ  ድርጅት «CPJ» ጠየቀ። በጥቃቱ የጋዜጠኞች ቡድኑን ያሰፈረዉን መኪና ሲያሽከረክር የነበረዉ ሱሊማን መሃመድ በደረሰበት ጉዳት ሲሞት ሌሎች አምስት መኪና ዉስጥ የነበሩ ሰዎች መቁሰላቸዉ ተያይዞ ተዘግቦአል። በቡድኑ ላይ ጥቃት የተፈጸመዉ የኤርትራዉ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በኢትዮጵያ ያደረጉትን ጉብኝት ለመዘገብ ቡድኑ ሐምሌ ስድስት ቀን ከድሬዳዋ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ ነበር ። «CPJ» እንደዘገበዉ ጋዘጠኞቹን ያሳፈረችዉ መኪና በኦሮሚያ ክልል ሚኤይሶ ከተማ ስትደረስ ማንነታቸዉ ያልታወቁ ሰዎች መኪናዋን አስቁመዉ ተሳፋሪዎቹን ደብድበዋል።

አዜብ ታደሰ

አርያም ተክሌ