5ኛዉ የአፍሪቃ እና የአዉሮጳ ኅብረት ጉባኤ
ሐሙስ፣ ኅዳር 21 2010ማስታወቂያ
ለሁለት ቀናት ያካሄዱት ጉባኤ የጋራ ትብብር ላይ ያተኩራል ቢባልም ዋና ትኩረቱ ስደትን መገደብ ላይ እንደሆነ ነዉ የሚነገረዉ። ከ80 የሚበልጡ ሃገራት መሪዎች በተሳተፉበት በዚህ ለአምስተኛ ጊዜ በተካሄደዉ የአፍሪቃ እና የአዉሮጳ ሃገራት ጉባኤ ማጠቃለያ ላይም በስደት እና በፀጥታ ጉዳይ ላይ ትብብራቸዉን ለማጠናከር ቃል ገብተዋል። የወጣት ትዉልዷ ቁጥር እያደገ መሄዱ የሚነገርላት አፍሪቃ የሥራ ዕድሎችን ማስፋፋት እስካልቻለች ድረስ ግን የስደት ጉዳይ አሁንም አሳሳቢ እንደሆነ እንደሚቀጥል ነዉ የሚነገረዉ። የዶቼ ቬለዋ ባርባራ ቬዝል የጻፈችዉን ይልማ ኃይለ ሚካኤል ከበርሊን እንደሚከተለዉ አጠናቅሮታል።
ባርባራ ቬዝል/ይልማ ኃይለ ሚካኤል
ሸዋዬ ለገሠ