54 ኢትዮጵያዉያን በኬንያ ታሰሩ1 ታኅሣሥ 2008ዓርብ፣ ታኅሣሥ 1 2008የኬንያ ፖሊስ በሕገ- ወጥ አገሪትዋ ዉስጥ የሚኖሩ ያላቸዉን 54 ኢትዮጵያዉያን ማሰሩ ተመለከተ። እንደ ፖሊስ ገለጻ፤ በኬንያ ናይሮቢ ካሳራኒ በሚባል አካባቢ ሦስት ክፍል ዉስጥ ሲኖሩ የነበሩ እነዚህ ኢትዮጵያዉያን የተያዙት ፖሊስ በደረሰዉ ጥቆማ እንደሆነ ገልጾአል።https://p.dw.com/p/1HM4sምስል Getty Images/AFP/T. Karumbaማስታወቂያ ነዋሪዉ እንዲህ ዓይነቱን ሕገ-ወጥ ነገር መጠቆሙ ለራስ ደሕንነት ነዉ ሲል፤ ማወደሱም ተዘግቦአል። ከአስር ወር በፊት እዚያዉ ኬንያ ናይሮኒ ዉስጥ ወደ ደቡብ አፍሪቃ ለመጓዝ ዝግጅት ላይ የነበሩ 101 ኢትዮጵያዉያንን ፖሊስ መያዙን ማስታወቁ አይዘነጋም። ፋሲል ግርማ አዜብ ታደሰ ሂሩት መለሰ