1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

54 ኢትዮጵያዉያን በኬንያ ታሰሩ

ዓርብ፣ ታኅሣሥ 1 2008

የኬንያ ፖሊስ በሕገ- ወጥ አገሪትዋ ዉስጥ የሚኖሩ ያላቸዉን 54 ኢትዮጵያዉያን ማሰሩ ተመለከተ። እንደ ፖሊስ ገለጻ፤ በኬንያ ናይሮቢ ካሳራኒ በሚባል አካባቢ ሦስት ክፍል ዉስጥ ሲኖሩ የነበሩ እነዚህ ኢትዮጵያዉያን የተያዙት ፖሊስ በደረሰዉ ጥቆማ እንደሆነ ገልጾአል።

https://p.dw.com/p/1HM4s
Kenia Sicherheitskräfte
ምስል Getty Images/AFP/T. Karumba

ነዋሪዉ እንዲህ ዓይነቱን ሕገ-ወጥ ነገር መጠቆሙ ለራስ ደሕንነት ነዉ ሲል፤ ማወደሱም ተዘግቦአል። ከአስር ወር በፊት እዚያዉ ኬንያ ናይሮኒ ዉስጥ ወደ ደቡብ አፍሪቃ ለመጓዝ ዝግጅት ላይ የነበሩ 101 ኢትዮጵያዉያንን ፖሊስ መያዙን ማስታወቁ አይዘነጋም።

ፋሲል ግርማ

አዜብ ታደሰ

ሂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ