125 ዓመት ዕድሜ ያስቆጠረው የካርል ዛይስ ድርጅት
ረቡዕ፣ ሚያዝያ 22 2006ማስታወቂያ
ሀገር ትሰኝ የነበረችው ሀገር ፣ ሳይንሳዊ ዕውቀትን ፣ ሥነ ቴክኒክን ለሕብረተሰብ ጠቀሜታ እንዲውል በየረድፉ ባደረገችው ምርምር በተለይ ከ 19ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ገደማ አንስቶ እስከ ሁለተኛው የዓለም ጦርነት ፤ ከዚያ ወዲህም ቢሆን፤ ለአያሌ ግኝቶች መሠረት ለመሆን መብቃቷ እሙን ነው። አገሪቱ ለሳይንስና ሥነ ቴክኒክ ምርምር ላቅ ያለ ግምት ከመስጠት የቦዘነችበት ጊዜ የለም።
ጀርመን ውስጥ ከድሮ ጀምሮ ፣ ከታወቁት ሳይንስንና ሥነ ቴክኒክን መሠረት አድርገው ከተቋቋሙት ድርጅቶች ወይም ኩባንያዎች መካከል፤ የዓይን መነጽር፤ ካሜራ ፤ ኢምንት ነገሮችን አጉልቶ የሚያሳይ መነጽር(ማይክሮስኮፕ)፤እጅግ ራቅ ብለው በኅዋ የሚገኙ የሰማይ አካላትን አቅርቦ የሚያሳይ ቴሌስኮፕ፣ለቀዶ ህክምናና ለመሳሰለው የሚጠቅሙ የረቀቁ ዘመናዊ መሣሪያዎችን ሠርቶ በማቅረብ እጅግ የታወቀው ካርል ዛይስ ነው። ድርጅቱ በመሥራቹ ስም ነው የሚጠራው።
ተክሌ የኋላ
ሸዋዬ ለገሠ