1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ድርድሩ አበቃ፣ ግን ይቀጥላል

ማክሰኞ፣ ሐምሌ 7 2012

የኢትዮጵያ የቴክኒክ ቡድን ሰብሳቢ ኢንጂነር ጌድዮን አስፋዉ እንደሚሉት ግን ተደራዳሪዎች ለፊርማ ከሚያበቃ ስምምነት ላይ ባይደርሱም የተስማሙባቸዉ ጉዳዮች አሉ።ኢትዮጵያ ግድቡን ዉኃ መሙላት ጀምራለች ለሚለዉ ጥያቄ ግን ኢንጂነሩ «የግድቡ ቁመት በጨመረ ቁጥር፣ ሙሌቱም ይጀመራል» በማለት አልፈዉታል።

https://p.dw.com/p/3fJcO
Äthiopien Grand Renaissance Damm
ምስል Reuters/t. Negeri

ድርድሩ ያለዉጤት አበቃ ግን ይቀጥላል

ኢትዮጵያ በዐባይ ወንዝ ላይ በምታስገነባዉ ግድብ ምክንያት ከግብፅ ጋር የገጠመችዉን ዉዝግብ ለማስወገድ የኢትዮጵያ፣የሱዳንና ግብፅ ባለስልጣናት ለአስራ አንድ ቀናት ያደረጉት ድርድር እንደከዚሕ ቀደሞቹ  ሁሉ ያለ ሁነኛ ሥምምነት አብቅቷል።በድርድሩ ላይ የተካፈሉት የኢትዮጵያ የቴክኒክ ቡድን ሰብሳቢ ኢንጂነር ጌድዮን አስፋዉ እንደሚሉት ግን ተደራዳሪዎች ለፊርማ ከሚያበቃ ስምምነት ላይ ባይደርሱም የተስማሙባቸዉ ጉዳዮች አሉ።ኢንጂነር ጌድዮን በአፍሪቃ ሕብረት አደራዳሪነት የሚደረገዉ ድርድር ወደፊት ይቀጥላል ብለዉ ይገምታሉ።ኢትዮጵያ ግድቡን ዉኃ መሙላት ጀምራለች ለሚለዉ ጥያቄ ግን ኢንጂነሩ «የግድቡ ቁመት በጨመረ ቁጥር፣ ሙሌቱም ይጀመራል» በማለት አልፈዉታል።ኢንጂነር ጌድዮንን ነጋሽ መሐመድ በስልክ አነጋግሯቸዋል።

ነጋሽ መሐመድ

አዜብ ታደሰ