ዴንማርክ፤ የአይሁዳዊያን ምኩራብ ፊት ለፊት ተኩስ
እሑድ፣ የካቲት 8 2007ማስታወቂያ
እንደ ፖሊስ ገለፃ ተጠርጣሪው የአይሁዳዊያን ምኩራብን ሲጠብቅ ለነበረ ወጣት ሞት ተጠያቂ ነው። ከዚህም በተጨማሪ በፖሊስ የተገደለው ተጠርጣሪ ይህ ከመሆኑ ከሰዓታት በፊት በአንድ ስብሰባ ላይ የተካፈሉ የ55 ዓመት ሰውንም ሳይገድል አልቀረም ተብሏል። በስብሰባው ላይ የተከፈተው ተኩስ ምናልባትም ኢላማ አድርጎ የነበረው ላርስ ቪልክስ የተባሉ የስላቅ ስእሎች ሰዓሊ ላይ ሳይሆን እንዳልቀረ ፖሊስ ገልጿል። ስዊዲናዊው ሰዓሊ ነብዩ መሐመድን የሚመለከቱ ስላቃዊ ምስሎችን ይስላሉ በሚል በተደጋጋሚ በሙስሊሞች ዘንድ ወቀሳ ቀርቦባቸው እና የጥቃት ኢላማም ሆነው እንደነበር ተገልጿል።
ልደት አበበ
ማንተጋፍቶት ስለሺ