1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይና የፖለቲካ ፓርቲዎች ውይይት

ረቡዕ፣ መስከረም 6 2013

ትናንት በጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት የተካሄደው እና በመጪው ሳምንት ይቀጥላል የተባለውን ውይይት የምመራው ከሆነ በጋራ ምክር ቤቱ የታቀፉ ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች እንዲሳተፉ አደርጋለሁ ሲል የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገለፀ። የትናንቱ ውይይት ሀገራዊ መግባባት በመፍጠር ላይ ያተኮረ እንደነበር ተሳታፊዎች ገልጸዋል።

https://p.dw.com/p/3iYpd
Äthiopien - Addis Abeba - City Churchill Road
ምስል DW/Y. Geberegziabehr

«ውይይቱ ሀገራዊ መግባባት በመፍጠር ላይ ያተኮረ ነበር»

ትናንት በጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት የተካሄደው እና በመጪው ሳምንት ይቀጥላል የተባለውን ውይይት የምመራው ከሆነ በጋራ ምክር ቤቱ የታቀፉ ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች እንዲሳተፉ አደርጋለሁ ሲል የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገለፀ። ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ጋር የተካሄደው ውይይት ሀገራዊ መግባባት በመፍጠር ላይ ያተኮረ እንደነበር ያነጋገርናቸው ተሳታፊ ፓርቲዎች ገልጸዋል። ከዚህ በፊት በነበረው ስብሰባ ላይ ሀምሳ ፖለቲከኞች ብቻ መሳተፋቸውም ታውቋል። ፓርቲዎቹ በቀጣይም በሕገ መንግሥትና ሕገ መንግሥታዊነት፣ በፖለቲካ ፓርቲዎች አደረጃጀት፣ በምርጫ እና መሰል ጉዳዮችን ላይ ለመወያየት ቀጠሮ ይዘዋል። ሰሎሞን ሙጬ ከአዲስ አበባ ዝርዝር ዘገባ አለው።

ሰሎሞን ሙጬ

ሸዋዬ ለገሠ

አዜብ ታደሰ