1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የጌድኦ ምሁራን ተቃውሞ 

ረቡዕ፣ ሐምሌ 8 2012

ምሁራኑ ጌድኦ በልዩ ዞን ይደራጃል በሚል በፌደራል መንግሥት አጥኚዎች የቀረበው ምክረ ሃሳብ ሕገ መንግሥታዊ መሠረት የሌለው የዞኑን መልክዐ ምድራዊ አቀማመጥን ያላገናዘበ ነው አሉ። ምሁራኑ የደቡብ ክልልን በ4 ወይም በ5 ቦታዎች በማዋቀር ወደ ነበረበት አደረጃጀት ይመለስ ቢባል እንኳን በቅድሚያ የሃገሪቱን ሕገ መንግሥት ማሻሻል ይጠይቃል ብለዋል።

https://p.dw.com/p/3fNV3
Karte Äthiopien englisch

የጌድኦ ምሁራን ተቃውሞ 

ሲዳማ በክልል ከተደራጀ በኋላ ከደቡብ ክልል የሚዋሰነው ድንበር ባለመኖሩ  ተነጥሎ የቀረው የጌድኦ ዞን አደረጃጀት በተለያየ ሁኔታ ሊታይ ይገባል ሲሉ የብሄሩ ምሁራን ጠየቁ።ሰሞኑን በዲላ ከተማ የመከሩት እነኚሁ ምሁራን ጌድኦ በልዩ ዞን ይደራጃል በሚል በፌደራል መንግሥት አጥኚዎች የቀረበው ምክረ ሃሳብ ሕገ መንግሥታዊ መሠረት የሌለው የዞኑን መልክዐ ምድራዊ አቀማመጥን ያላገናዘበ ነው ሲሉ ተቃውመውታል። ምሁራኑ በዚሁ ውይይታቸው ላይ አሁን ያለውን የደቡብ ክልል በ4 ወይም በ5 ቦታዎች በማዋቀር በፊት ወደ ነበረበት አደረጃጀት ይመለስ ቢባል እንኳን በቅድሚያ የሃገሪቱን ሕገ መንግሥት ማሻሻል ይጠይቃል ብለዋል።ውይይቱን የተከታተለው የሃዋሳው ወኪላችን ሸዋንግዛው ወጋየሁ ተከታዩን ዝርዝር ልኮልናል።
ሸዋንግዛው ወጋየሁ
ኂሩት መለሰ
ነጋሽ መሐመድ