የወይዘሮ ሙፈሪያት ማስጠንቀቂያ | ኢትዮጵያ | DW | 20.08.2019
  1. Inhalt
  2. Navigation
  3. Weitere Inhalte
  4. Metanavigation
  5. Suche
  6. Choose from 30 Languages
ማስታወቂያ

ኢትዮጵያ

የወይዘሮ ሙፈሪያት ማስጠንቀቂያ

ወይዘሮ ሙፈሪያት በፓርቲያቸዉ ጉባኤ ማብቂያ ላይ እንደተናገሩት አንዳድ የደኢሕዴን ባለስልጣናት ከፓርቲዉ ዉጪ ያሉ «አለቆቻቸዉ» ላላሏቸዉ ወገኖች አጎብዳጆች ናቸዉ

ደኢሕዴንን የሚያዉኩ «ጥርግ ማለት ይችላሉ» ሙፈሪያት

የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ደኢሕዴን) ሊቀመንበር ሙፈርያት ካሚል የፓርቲያቸዉን ባለስልጣናት «በሁለት ቢላ የሚበሉ፣ አድሐሪ» በማለት ወቀሱ። ከደቡብ ኢትዮጵያ ገዢ ፓርቲ ሊቀመንበርነት በተጨማሪ የፌደራሉን የሰላም ሚንስትርነት ስልጣን ደርበዉ የያዙት ወይዘሮ ሙፈሪያት በፓርቲያቸዉ ጉባኤ ማብቂያ ላይ እንደተናገሩት አንዳድ የደኢሕዴን ባለስልጣናት ከፓርቲዉ ዉጪ ያሉ «አለቆቻቸዉ» ላላሏቸዉ ወገኖች አጎብዳጆች ናቸዉ። የሲዳማን ጨምሮ በተለያዩ የደቡብ ኢትዮጵያ ዞኖች የሚኖሩ የተለያዩ ጎሳ ፖለቲከኞች የክልልነት አስተዳደር በይፋ መጠየቅ ከጀመሩ ወዲሕ ደኢሕዴን ክፉኛ ተዳክሟል ነዉ የሚባለዉ። ወይዘሮ ሙፈሪያት እንደሚሉት የፓርቲዉን ሥራና አሰራር የሚያዉኩ ባለስልጣናት «ጥርግ» ማለት ይችላሉ።«ግን» አሉ ሊቀመንበሯ  በቅድሚያ የኃላፊነትን ሒሳብ አወራርዶ ነዉ ታዲያ።

 ሸዋንግዛዉ ወጋየሁ 

ነጋሽ መሐመድ

አዜብ ታደሰ

Audios and videos on the topic