1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኦሮሚያ ክልል መንግስት ከፌዴራል ኃይሎች ጋር የቅንጅት እርምጃ ጀመሩ

ሰኞ፣ ሚያዝያ 3 2014

በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች እየተስተዋሉ ያሉትን የሰላምና ፀጥታ ችግሮች እልባት ለመስጠት የክልሉ እና የፌዴራል መንግስት ኃይላት የተቀናጀ እርምጃ እየወሰዱ መሆኑን አስታወቀ፡፡፡ የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረንስ ኦፌኮ በበኩሉ የኃይል እርምጃ ህዝቡን የሚጎዳ በመሆኑ ለፖለቲካዊ ችግሮች ፖለቲካዊ መፍትሄ እንዲፈለግ ጠይቋል፡፡

https://p.dw.com/p/49n3d
Äthiopien Hailu Adugna
ምስል Seyoum Getu/DW

በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች እየተስተዋሉ ያሉትን የሰላምና ፀጥታ ችግሮች እልባት ለመስጠት የክልሉ እና የፌዴራል መንግስት ኃይላት የተቀናጀ እርምጃ እየወሰዱ መሆኑን አስታወቀ፡፡፡

የክልሉ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ዛሬ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ እየተወሰደ ያለው እርምጃ የጸጥታ መሻሻልን እያመጣ ነው ብሏል፡፡

በሌላ በኩል መንግስት በኦሮሚያ እየወሰደ ያለው የኃይል እርምጃ ህዝቡን የሚጎዳ በመሆኑ ለፖለቲካዊ ችግሮች ፖለቲካዊ መፍትሄ እንዲፈለግ ሲል የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግሬስ (ኦፌኮ) ጠይቋል፡፡

ስዩም ጌቱ 

ታምራት ዲንሳ

ማንተጋፍቶት ስለሺ