1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮ-ሱዳን ዉዝግብ እንደቀጠለ ነዉ

ማክሰኞ፣ ጥር 4 2013

የሱዳን ጦር የኢትዮጵጵያን ድንበር ዘልቆ ተጨማሪ ግዛቶች መቆጣጠሩን የኢትዮጵያ ዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር ዛሬ አስታዉቋል።የዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ ዲና ሙፍቲ ዛሬ ለጋዜጠኞች እንደነገሩት የሱዳን መንግስት የኢትዮጵያ ግዛቶችን መዉረሩን እንዲያቆም ኢትዮጵያ በተደጋጋሚ ብትጠይቅም እስካሁን ሰሚ አላኘችም።

https://p.dw.com/p/3npS7
Äthiopien Dina Mufti

የኢትዮጵያና የሱዳን ዉዝግብ

የኢትዮጵያና የሱዳን መንግስታት በድንበር ግዛት ይገባኛል ሰበብ የገጠሙት ዉዝግብ አሁንም እንደቀጠለ ነዉ።የሱዳን ጦር የኢትዮጵጵያን ድንበር ዘልቆ ተጨማሪ ግዛቶች መቆጣጠሩን የኢትዮጵያ ዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር ዛሬ አስታዉቋል።የዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ ዲና ሙፍቲ ዛሬ ለጋዜጠኞች እንደነገሩት የሱዳን መንግስት የኢትዮጵያ ግዛቶችን መዉረሩን እንዲያቆም ኢትዮጵያ በተደጋጋሚ ብትጠይቅም እስካሁን ሰሚ አላገኘችም።አምባሳደር ዲና አክለዉ እንዳሉት ሱዳንና ግብፅ የሕዳሴ ግድብ ድርድርን ለማጓተት፣ ሱዳን የተጠለሉ ኢትዮጵያዉያን ወደ ሐገራቸዉ እንዳይመለሱ ለማድረግም እያሴሩ ነዉ።

 ሠለሞን ሙጬ 

ነጋሽ መሐመድ

ኂሩት መለሰ