1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአውሮጳ ኅብረትና አዲሱ የአሜሪካን ፕሬዝዳንት 

ሐሙስ፣ ጥር 13 2013

ለፕሬዝዳንት ባይደንና ለአዲሷ ም/ፕሬዝዳንት ካማላ ሃሪስ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክቱን ያስተላለፈው የአውሮጳ ኅብረት የቀድሞውን የኅብረቱንና የአሜሪካን ግንኙነት ማደሻው ጊዜ አሁን ነው ሲል አስታውቋል።የኅብረቱ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርዙላ ፎን ዴር ላየን አውሮጳ ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር ግንኙነታቸውን ለማዳስ ኅብረቱ ዝግጁ መሆኑን አስታውቀዋል።

https://p.dw.com/p/3oFX3
USA Washington | Joe Biden unterschreibt Kabinettsnominierungen im Kapitol
ምስል Jim Lo Scalzo/UPI Photos/imago images

የአውሮጳ ኅብረትና አባል ሃገራት ለለአዲሱ የአሜሪካን ፕሬዝዳንት 

የዓለም መንግሥታት፣46ተኛው የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት በመሆን ትናንት ቃለ መሃላ ለፈጸሙት ለአዲሱ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን የመልካም ምኞት መግለጫዎችን እያስተላለፉ ነው።በዚሁ መግለጫቸውም ከባይደን ጋር አብሮ ለመስራት ፍላጎት እንዳላቸው አስታውቀዋል።ለፕሬዝዳንት ባይደንና ለአዲሷ ምክትል ፕሬዝዳንት ካማላ ሃሪስ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክቱን ያስተላለፈው የአውሮጳ ኅብረት የቀድሞውን የኅብረቱንና የአሜሪካን ግንኙነት ማደሻው ጊዜ አሁን ነው ሲል አስታውቋል።የኅብረቱ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርዙላ ፎን ዴር ላየን አውሮጳ ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር ግንኙነታቸውን ለማዳስ ኅብረቱ ዝግጁ መሆኑን አስታውቀዋል።

ገበያው ንጉሴ
ኂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ