1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ኮሮና እና ጥብቅ የዝዉዉር ገደብ በጀርመን

ማክሰኞ፣ ጥር 4 2013

ትምህርት ቤቶች የስፖርት ማዕከላት ቡና እና ምግብ ቤቶች ተዘግተዋል። አንድ ሰዉ አብሮ ከሚኖረዉ የቤተሰብ አባላት ሌላ ማግኘት የሚችለዉ አንድን ሰዉ ብቻ ነዉ። ተማሪዎች በየቤታቸዉ በኢንተርኔት ትምህርታቸዉን ቀጥለዋል።

https://p.dw.com/p/3npZ5
BdT Schnee und Eis in Deutschland Landschaft
ምስል Nicolas Armer/dpa/picture alliance

የኮሮና ሥርጭት በጀርመንና አዲሱ እገዳ

በጀርመን የኮሮና ተኅዋሲ ስርጭትን ለመግታት አዲስ የተጣለዉ  ጥብቅ የዝዉዉር ገደብ ከትናንት ከሰኞ ጥር 3 ቀን፣ 2013 ዓ.ም ጀምሮ ገቢራዊ ሆኗል። ትምህርት ቤቶች የስፖርት ማዕከላት ቡና እና ምግብ ቤቶች ተዘግተዋል። አንድ ሰዉ አብሮ ከሚኖረዉ የቤተሰብ አባላት ሌላ ማግኘት የሚችለዉ አንድን ሰዉ ብቻ ነዉ። ተማሪዎች በየቤታቸዉ በኢንተርኔት ትምህርታቸዉን ቀጥለዋል። አዲሱ ደንብ   ያዘነዉ የጎርጎረሳዉያን ጥር ወር መጨረሻ  ድረስ ተፈፃሚ ይሆናል።ደንቡ ይራዘማል የሚል ግምትና አስተያየትም ከወዲሁ እየተሰጠ ነዉ። ጀርመን ዉስጥ ባለፉት 24 ሰዓታት ብቻ 863 ሰዎች በኮቪድ 19 ሞተዋል።የኮሮና ተሕዋሲ ጀርመን ዉስጥ የገደለዉ ሰዉ ቁጥር ወደ   42 ሺህ ደርሶአል። በተኅዋሲ የተያዘዉ ሰዉ ቁጥር  ሁለት ሚሊዮን ተጠግቷል።

አዜብ ታደሰ 

ይልማ ኃይለሚካኤል 

ነጋሽ መሐመድ