እስራኤልና ዩናይትድ ስቴትስ በኢራን ላይ የከፈቱት ጦርነትና የአሜሪካኖች አስተያየት
ማክሰኞ፣ የካቲት 24 2018
ማስታወቂያ
እስራኤልና ዩናይትድ ስቴትስ በ8 ወራት ዉስጥ ለሁለተኛ ጊዜ በኢራን ላይ የከፈቱት ጦርነት መካከለኛዉ ምሥራቅን እያመሰቃቀለዉ ነዉ።ኢራን የሁለቱን ጥብቅ ወዳጆች ጥቃት ለመበቀል እስራኤልንና የዩናይትድ ስቴትስ ንብረቶች ያሉባቸዉን ሐገራት በሙሉ እየመታች ነዉ።ጦርነቱ አድማሱን አስፍቶ የሊባኖሱ ደፈጣ ተዋጊ ቡድን ሒዝቦላሕ እስራኤል ሲመታእስራኤል ባንፃሩ ሊባኖስን እየደበደበች ነዉ።4ኛ ቀኑን በያዘዉ ጦርነት በመቶ የሚቆጠሩ የተለያዩ ሐገራት ዜጎች ተገድለዋል።አብዛኞቹ ኢራናዉያን ናቸዉ።የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ጦርነቱ ገና መጀመሩ ነዉ ይላሉ።ጥናቶች እንደሚያመለክቱት ግን አብዛኛዉ የአሜሪካ ህዝብ ጦርነቱን አይደግፍም።
አበበ ፈለቀን
ነጋሽ መሐመድ
አዜብ ታደሰ