ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን። ስለዚሁ ጉዳይ ተጨማሪ መረጃዎችን ከሰነድ አጠባበቅ መግለጫችን ማግኘት ይችላሉ።
ኢትዮጵያ ምስራቅ አፍሪቃ ውስጥ የምትገኝ ሀገር ናት። ኤርትራ፣ ሱዳን፣ደቡብ ሱዳን፣ ኬንያ ፣ ሶማሊያ እና ጅቡቲ ያዋስኗታል። 1.1 ሚሊዮን ካሬ ኪሎ ሜትር ስፋት ያላት ሲሆን ከ100 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ አላት።
ኢትዮጵያ በአውሮጳ ቅኝ አገዛዝ ሥር ያልወደቀች ብቸኛዋ አፍሪቃዊት ሀገር ነች።
የአፍሪቃ እና የአውሮጳ ዋንጫ የማጣሪያ ጨዋታዎች ዛሬም ቀጥለዋል ። ምሽቱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከጊኒ ጋር እዛው ሞሮኮ ውስጥ ያደርጋል ። ክሪስቲያኖ ሮናልዶ በዓለም አቀፍ ውድድሮች በመሰለፍ እና ለብሔራዊ ቡድኑ በርካታ ግቦችን በማስቆጠር ክብረወሰን ሰብሯል ። የአርጀንቲና እግር ኳስ ፌዴሬሽን የማሰልጠኛ ማእከሉን በሊዮኔል ሜሲ ስም ሰይሟል ።
ኢትዮጵያ ዛሬ ርዕሰ ከተማ አዲስ አበባን ጨምሮ ጋዜጠኞች፣ የማሕበራዊ መገናኛ ዘዴ ተቺዎች፣ አቀንቃኞች፣ ባለሐብቶችና ሌሎች ዜጎችም በጠራራ ፀሐይ የሚታገቱ፣ የሚደበደቡ፣ የሚዘረፉባት፣ ፖለቲከኞች፣ምሑራን፣ጋዜጠኞች፣የኃይማኖት መሪዎች፣ የመብት ተሟጋቾች ሳይቀሩ ጎሳና ኃይማኖት እየመረጡ እርስበርስ የሚካሰሱ፣የሚወዛገቡባት ሐገር ናት።
የአሜሪካ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ሃገራቸዉ ከአፍሪቃ ጋር ያላትን ግንኙነት ያጠናክራል ያሉትን ጉብኝት በማካኼድ ላይ ይገኛሉ። የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በቅርቡ በኢትዮጵያና ኒጀር ጉብኝት ካደረጉ በኋላ፣ ምክትል ፕሬዚዳንት ካማላ ሃሪስ በሦስት የአፍሪቃ ሃገራት ጉብኝታቸዉን ጀምረዋል። የባለሥልጣኑ ጉብኝት አንደምታ ምን ይሆን?
በኢትዮጵያ ውስጥ በተለይም በኦሮሚያ ያሉትን የስኳር አምራች ፋብሪካዎችን እየፈተነ የሚገኘው የፀጥታ ችግር በምርቱ የገበያ ላይ እጥረት ካስከተሉ አበይት ምክኒያቶች ናቸዉ፡፡ በዚሁ ችግር በአከባቢው በሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች ጥቃት ደርሶበት ሁለት ጊዜ ስራ ያቆመዉ የአርጆ ዴዴሳ ስኳር ፋብሪካ በፀጥታ ችግሩ መፈተኑ ይጠቀሳል፡፡
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት እስከ ግንቦት 30 2015 ዓ.ም በክልሉ ምርጫ እንዲካሄድ ጥሪ አቀረበ፡፡ በምርጫ ቦርድ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ቀረበ የተባለው የፖለቲካ ፓርቲዎች ምክረ ሀሳብ እንዳልደረሰው ጠቋሟል፡፡
ኢትዮጵያ ለሽግግር ፍትህ ዝግጁ ነች? የፍትህ ሚኒስቴር ካቋቋመው ከፍተኛ የባለሙያዎች ቡድን አቶ ምስጋናው ሙሉጌታ እና ዶ/ር ማርሸት ታደሰ፤ በሐርቫርድ ዩኒቨርሲቲ የህግ ትምህርት ቤት የሰብዓዊ መብቶች መርሐ-ግብር ተባባሪ ዳይሬክተር ዶክተር አባድር ኢብራሒም እና ዘ-ሔግ በሚገኝ ፍርድ ቤት በአማካሪነት የሚሰሩት አቶ ካሳሁን ሞላ በውይይቱ ተሳትፈዋል
ከግዚያዊ አስተዳደሩ ምን ትጠብቃላችሁ በሚል ያነጋገርናቸው የመቐለ ዩኒቨርሰቲ የአስተዳደር ትምህርት ክፍል አስተማሪው ዶክተር ተክላይ ተስፋይ፥ በትግራይ ካለው ነባራዊ ሁኔታ አንፃር በመነሳት ቅድሚያ መፈፀም ያለበት፣ በትግራይ ያሉ የውጭ ሃይሎች ማስወጣት እና የተፈናቀለው በሚልዮኖች የሚቆጠር ህዝብ መመለስ ሊሆን ይገባል ብለዋል።
የማኅበራዊ መገናኛ ዘዴ ተጠቃሚው በየዕለቱ ሃሳቡን የሚሰነዝርበት አዳዲስ ጉዳይ መከሰቱ ቀጥሏል።
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ-መስተዳደር ሆነው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ትናንት መሾማቸው የተገለጠው አቶ ጌታቸው ረዳ ዛሬ በሰጡት መግለጫ፥ የትግራይ ክልል ግዛታዊ አንድነትን ለማስጠበቅ እንደሚሠሩ ተናገሩ ። የተፈናቀሉ ያሏቸውን መልሶ ወደ ቀዬአቸው የመመለስ ተግባራት እና ሌሎች ቀዳሚ አጀንዳዎችን እንደሚሠራባቸውም ዐስታውቀዋል ።
"የዚህ ጦርነት ተሳታፊዎች ብዙ ናቸው። ዓላማቸውም እንደዚሁ በጣም የተለያየ ነው። ትግራይ ላይ ወይም ሕወሓት ላይ ተመሳሳይ አቋም የነበራቸው አካላት አብረው ተሰልፈዋል እና ከኢትዮጵያ መንግሥት በኩል እነዚህን አካላት አሁንም አንድ ላይ አስተባብሮ ወደ ሰላም ስምምነቱ ማስገባት እና ተገዢ ለማድረግ አስቸጋሪ እንደሚሆን ይገባኛል"
የኢትዮጵያ ፌድራል መንግሥት መስሪያ ቤቶች የ2016ን በጀት ሲያዘጋጁ "ከውጭ ሊገኝ የሚችልን ዕርዳታ እና ብድር በማሰብ" ሊሆን እንደማይገባ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አሕመድ ሽዴ አሳስበዋል። የፕሪቶሪያ የሰላም ሥምምነት እና የሽግግር ፍትኅ አተገባበር ምዕራባውያን የከለከሉትን እርዳታ እና ብድር ለመፍቀድ ቅድመ-ሁኔታ አድርገዋል።