በቀድሞ የብሔራዊ መረጃ እና ደኅንነት አገልግሎት ኃላፊና ሠራተኞች ላይ የቀረበው ክስ
ረቡዕ፣ ሚያዝያ 30 2011
ማስታወቂያ
የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት፤ ልደታ ምድብ፤ አንደኛ ችሎት በቀድሞ የብሔራዊ መረጃ እና ደኅንነት አገልግሎት ኃላፊና ሠራተኞች ላይ የቀረበውን ክስ ዛሬም ማድመጡን ቀጥሏል። በዛሬው ችሎት የአንደኛውን ተከሳሽ የአቶ ጌታቸው አሰፋን ጨምሮ ከ5 ተኛ እስከ 19ኛ የተዘረዘሩ ተካሶችን ክስ አዳምጧል። ችሎቱን የተከታተለው የአዲስ አበባው ወኪላችን ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር በተጠርጣሪዎች ላይ የቀረበው ክስ ተመሳሳይነት እንዳለው ተናግሯል። ችሎቱ አቶ ጌታቸው አሰፋን ጨምሮ ፍርድ ቤት ያልቀረቡ አራት ተጠርጣሪዎች የፌደራል ፖሊስ ባሉበት መጥሪያ እንዲሰጣቸው አቃቤ ሕግ በጠየቀው መሠረት ነገ ችሎት ያልቀረቡትን ተከሳሾች በተመለከተ ለፖሊስ ትዕዛዝ ለመስጠት ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። ስለ ዛሬው የፍርድ ቤት ውሎ ስቱድዮ ከመግባቴ በፊት ዬሐንስን በስልክ አነጋግሬው ነበር።
ዮሐስ ገብረ እግዚአብሔር
ኂሩት መለሰ
ነጋሽ መሐመድ