በምዕራብ ሸዋ ዞን በተቀሰቀሰ ግጭት ከ20 በላይ ሰዎች ተገደሉ | ኢትዮጵያ | DW | 22.11.2021
  1. Inhalt
  2. Navigation
  3. Weitere Inhalte
  4. Metanavigation
  5. Suche
  6. Choose from 30 Languages
ማስታወቂያ

ኢትዮጵያ

በምዕራብ ሸዋ ዞን በተቀሰቀሰ ግጭት ከ20 በላይ ሰዎች ተገደሉ

በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ኖኖ ወረዳ ባለፈው ዓርብ በደረሰ ጥቃት ከ20 በላይ ሰዎች መገደላቸውን የዓይን እማኞች ተናገሩ። በወረዳው በመረዳዳት እና ተሳስበው በሚኖሩ ሁለት ብሔሮች መካከል ልዩነት ለመፍጠር በተንቀሳቀሱ አካላት ተከስቷል በተባለው በዚህ ግጭት በተለያዩ የዕድሜ ክልሎች የሚገኙ ሰዎች የጥቃቱ ሰለባ መሆናቸው ተገልጿል።

በምዕራብ ሸዋ ዞን በተቀሰቀሰ ግጭት ከ20 ባላይ ሰላማዊ ሰዎች ተገደሉ

በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ኖኖ ወረዳ ባለፈው ዓርብ በደረሰ ጥቃት ከ20 በላይ ሰዎች መገደላቸውን የአይን እማኞች ተናገሩ። በወረዳው በመረዳዳት እና ተሳስበው በሚኖሩ ሁለት ብሔሮች መካከል ልዩነት ለመፍጠር በተንቀሳቀሱ አካላት ተከስቷል በተባለው በዚህ ግጭት በተለያዩ የዕድሜ ክልሎች የሚገኙ ሰዎች የጥቃቱ ሰለባ መሆናቸውን ነዋሪዎች ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል። በጥቃቱ ቤተሰቦቻቸውን ያጡ እና  በአከባቢው ይኖሩ የነበሩ የአማራ እና የኦሮሞ ብሔር ተወላጆች በተለይም ጥቃቱ ከተፈጸመበት መቱ ስላሴ ቀበሌ ቀዬያቸውን ጥለው መሰደዳቸውን ባለሥልጣናት አረጋግጠዋል። ግጭቱ የብሔር ሳይሆን የፖለቲካ ፍላጎት ያላቸው አካላት እንደፈጸሙት  የዞኑ አስተዳዳሪ ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል። ።  የጸጥታ ኃይሎች በአከባቢው  ተሰማርተው ማረጋጋታቸውንም አስረድተዋል።

ስዩም ጌቱ 

ታምራት ዲንሳ

ሸዋዬ ለገሰ

 

Audios and videos on the topic