ጥንታዊ የብራና ጽሑፎች ጥናት በጀርመን
እሑድ፣ መስከረም 26 2006ማስታወቂያ
ጀርመን የኢትዮጵያ ባህል ቋንቋ ጥናት በአዉሮጳ እንዲጀመር ያደረገች የመጀመርያዋ አዉሮጳ ሀገር መሆንዋ ይታወቃል። በሀንቡርግ ዩንበርስቲ የሚገኘዉ የኢትዮጵያ ጥናት የትምርት ክፍል በአፍሪቃ ቋንቋዎች እና ባህሎች ላይ ትምህርት የሚሰጥ ሲሆን በኢትዮጵያ ቋንቋዎች የአማርኛ የግዕዝ አልፎ አልፎ የትግርኛ እና የኦሮምኛ ቋንቋ ትምህርት ይሰጣል። በኢትዮጵያ የብራና ጽሑፎች ላይ ጥናትና ምርምር ይካሄዳል። በጀርመን ሀንቡርግ ከተማ በሚገኘዉ የአፍሪቃ በተለይም በኢትዮጵያ ጥናት የትምህርት ክፍል ዉስጥ በምርምር ሥራና የPHD ትምህርታቸዉን በመከታተል ላይ ያሉት አቶ አብርሃም አዱኛ በዕለቱ ዝግጅታችን ጋብዘናል!
አዜብ ታደሰ
ሂደት መለሰ