1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ጤናና አካባቢ ጥበቃ

ማክሰኞ፣ ጥር 5 2001

ሂሮሺማና ናጋሳኪ በተሰኙት ሁለት የጃፓን ከተሞች ላይ አሜሪካ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት የአቶሚክ ቦንቦችን ከጦር አውሮፕላኖቿ ስትወረውር፤ በከተሞቹ ይኖሩ የነበሩ ሰባ ሺህ ኮርያውያን ተቀጥፈዋል። አርባ ሺዎቹ ደቡብ ኮርያውያን ደግሞ ከአቶሚክ ቦንቡ ፍንዳታ በኋላ በተከሰተባቸው የጤና መታወክ ውስብስብነት የተነሳ በሂደት አልቀዋል።

https://p.dw.com/p/GXi9
1945 ዓ.ም. ሂሮሺማ
1945 ዓ.ም. ሂሮሺማምስል AP
አደገኛ የወፍ ጉንፋን በቻይና መልኩን ቀይሮ ከሰው ወደ ሰው ሊተላለፍ ነው ተብሏል። ገዳዩ የኢቦላ ቫይረስ ከኮንጎ ወደ ጎረቤት አገር አንጎላ እንዳይገባ ተሰግቷል። ኤድስን አስመልክቶ በአፍሪቃ መጠነኛ መሻሻል መታየቱና፤ የሁለተኛው ዓለም ጦርነት የሂሮሺማና ናጋሳኪ የአቶሚክ ቦንብ ጥፋት የጨረር ጉዳተኛ አዛውንት ኮሪያውያን የጤንነት ሁኔታ በተመለከተ ቅኝት ይኖረናል፤ በዛሬው የጤናና አካባቢ ጥበቃ ዝግጅታችን።