አራት የልዩ ኃይል አባላት ተገደሉ
ዓርብ፣ መጋቢት 27 2011ማስታወቂያ
በአማራ ክልል በከሚሴ አካባቢ በተነሳ ግጭት የክልሉ ልዩ ኃይል አባላት ሕይወት መጥፋቱን የአማራ ክልል መንግሥት ገለጠ፡፡ የክልሉ ቃል አቀባይ ለዶቼቬለ DW እንደተናገሩት የልዩ ኃይል አባላት የተገደሉት ሀሰተኛ ባሉት ወሬ ሰበብ በታጣቂዎች በተፈጸመባቸው ጥቃት ነው። በጥቃቱ የተጎዱ ሌሎች ሰዎች ደግሞ በደሴ ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸው ነው። ከመካከላቸው አንዳንዶቹ በአስጊ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ የደሴ ሆስፒታል አስታውቋል። ዓለምነው መኮንን ከባሕር ዳር ዘገባ ልኮልናል።
አለምነው መኮንን
ኂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ