ግብፅና አፍሪቃ ኅብረት
ሰኞ፣ ሐምሌ 15 2005
ከአፍሪቃ አንድነ ት ድርጅት (አፍሪቃ ኅብረት) መሥራች አባል ሃገራት አንዷ፣ ግብፅ ፣ በቅርቡ በህዝብ ተመርጠው የነበሩት ፕሬዚዳንቷ ሙሐመድ ሙርሲ ከሥልጣን እንዲወገዱ በተደረገበት እርምጃ ሳቢያ ፤ ግብፅ ባለፈው ሰኔ 28 ቀን 2005 ዓ ም፤ለጊዜው መታገዷ ተገቢ አይደለም ሲሉ የግብፅ ተወካይ ሞና ኦማር ገለጡ። የአፍሪቃ ኅብረት ያቋቋመው ቡድን የግብጽን ተጨባጫ ሁኔታ አጥንቶ ካቀረበ በኋላ ውሳኔው እንደገና እንደሚመረመር ድላሚና ዙማ ገልጸዋል። የግብፅ ልዩ ልዑክና ድላሚና ዙማ፤ ከተወያዩ በኋላ በከፈፍተና ደረጃ የተዋቀረ የአፍሪ ኅብረት አጥኚ ቡድን ወደ ግብፅ በመጓዝ፤ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ወገኖች ሁሉ ጋ ተገናኝቶ ከተነጋገረ በኋላ ተመልሶ ስለተልእኮው ለአፍሪቃ ኅብረት የሰላምና ፀጥታ ም/ቤት ዘገባውን እንዲያቀርብ ተስማምተዋል።
የግብፅ ተወካይ ሞና ኦማር---
«የወቅቱን የግብፅ ሁኔታ በተመለከተ የአፍሪቃ ኅብረት የሰላምና የፀጥታ ም/ቤት የወሰደው እርምጃ አሳስቦናል ፣ አሳዝኖናል። ምክንያቱም ስለተጨባጩ የግብፅ ይዞታ ግንዛቤ የማጣት ችግር አጋጥሞአልና!እዚህ የመጣነው፤ በቅርቡ የተካሄደው አብዮት የህዝባዊ መነሣሣት ውጤት እንጂ፤ ህገ-ወጥ የህገ -መንግሥት ለውጥ እንዳይደለ ለማስረዳት ነው።»
የአፍሪቃ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ፤ ተከታዩን ምላሽም ሆነ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
«አጥኚው ቡድን ሳይመለስ ውሳኔ ማሳለፍ አንችልም። አጥኚው ቡድን ለሰላምና ፀጥታው ም/ቤትዘገባውን ያቀርባል። ምክንያቱም የሰላምና ጸጥታው ም/ቤት ነውና መጀመሪያውንም አጥኚው ቡድን እንዲቋቋም ያደረገው። ቡድኑ የጥናት ውጤቱን ሲያቀርብ ያን መነሻ በማድረግ ተገቢ የሆነውን እርምጃ እንወስዳለን።»
ተክሌ የኋላ
አዜብ ታደሰ
አርያም ተክሌ