1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የጋዜጠኛ ጌታቸዉ ሽፈራዉ ብይንና በኤሬቻ አደጋ ሁለት ሰዎች መከሰሳቸዉ 

ዓርብ፣ ግንቦት 18 2009

የሰማያዊ ፓርቲ ስልሳን የሆነዉ የነገረ ኢትዮጵያ ዋና አርታኢ ጋዜጠኛ ጌታቸዉ ሽፈራዉ የአንድ ዓመት ከስድስት ወር እስራት ተፈረደበት። ጠበቃ አመሃ መኮንን ዛሬ ለዶይቼ ቬለ በሰጡት መግለጫ ጋዜጠኛ ጌታቸዉ ሽፈራዉ እስር ቤት አንድ ዓመት ከአምስት ወር በማሳለፉ በአመክኖ ይፈታል ብለን እናስባለን ሲሉ አስታውቀዋል።

https://p.dw.com/p/2deIq
Äthiopien Journalist Getachew Shiferaw
ምስል Blue Party Ethiopia

xxxÄthiopien-Journalist 18-Monats-Gefängnis&Zwei Männer _Errecha Charge - MP3-Stereo

 ክሱን የመብት ተሟጋቾች ፕረስ ነፃነት ላይ የተሰነዘረ ጥቃት ብለዉታል። እንደ አዣንስ ፍራንስ ፕረስ ዘገባ ከሆነም፤ ካለፈዉ ዓመት ታኅሳስ ወር ጀምሮ በእስር ላይ የሚገኘዉ ጋዜጠኛ ጌታቸዉ፤ ከተያዘበት አንስቶ ጊዜዉ ሲሰላ በቅርቡ ሊፈታ ይችላል። ዛሬ አዲስ አበባ ላይ በዋለ ሌላ ችሎት በኢሬቻ በዓል ላይ ለተፈጠረዉ ትርምስ ምክንያት ናቸዉ የተባሉ ሁለት ሰዎች በአሸባሪነት ክስ እንደተመሰረተባቸዉ ታዉቋል። ይህን ክስ አስመልክቶ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ሙላቱ ገመቹ፤ ክሱ ለኛ አዲስ ነዉ የምናጠናዉ ይሆናል ሲሉ ተናግረዋል። ሙሉዉን ዝርዝር ዘገባ የድምፅ ማድመጫ ማዕቀፉን በመቻን ያድምጡ።

አዜብ ታደሰ

አርያም ተክሌ