በየአምስት ዓመቱ በሚደረገው የፕሬዚደንቱ ምርጫ ላይ ሶሻል ዴሞክራትዋ ፕሮፌሰር ወይዘሮ ጊዚነ ሽቫን እና የተቃዋሚው የአረንጓዴዎቹ ፓርቲ አባልና የተንቀሳቃሽ ስዕል ተዋናይ የሆኑት ፔተር ዞዳን ከአምስት ዓመት ወዲህ በስልጣን በሚገኙት ፕሬዚደንት ሆርስት ከለር አንጻር በተፎካካሪነት ቀርበዋል። የጀርመን ህዝብ ደግሞ በየአራት ዓመቱ እንደሚያደርገው ሁሉ የፊታችን መስከረም አዲስ ምክር ቤት ይመርጣል።
YHH/AA