የ«CPJ» ዓመታዊ ዘገባ
ማክሰኞ፣ ታኅሣሥ 4 2009ማስታወቂያ
ኢትዮጵያ ጋዜጠኞችን በማሰር፤በመክሰስ እና ማንገላታት፤ የመናገርና የመፃፍ ነፃነትን በማፈን በግንባር ቀደምትነት ከሚጠቀሱ ሰወስት የአፍሪቃ ሐገራት አንዷ መሆኗን ዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት CPJ አስታወቀ።ድርጅቱ ትናንት ባወጣዉ ዓመታዊ ዘገባዉ እንዳስታወቀዉ በርካታ ጋዜጠኞችን በማሰር ከዓለም አንደኛ ቱርክ፤ ሁለተኛ ቻይና ሆነዋል።ከሁለቱ ሐገራት ጋር ሲወዳደር ብዙ ጋዜጠኞችና መገናኛ ዘዴዎች የሌሉባቸዉ የምስራቅ አፍሪቃ ሐገራት ከ3 እስከ አምስት ያለዉን ሥፍራ ይዘዋል።ግብፅ፤ኤርትራ እና ኢትዮጵያ።የዋሽግተን ዲሲዉ ዘጋቢያችን መክብብ ሸዋ ዝርዝር ዘገባ አለዉ።
መክብብ ሸዋ
ነጋሽ መሐመድ
ሸዋዬ ለገሰ