የCPJ ሽልማት ለኢትዮጵያዊዉ ጋዜጠኛ
ማክሰኞ፣ ኅዳር 14 2003ማስታወቂያ
አዉራምባ-ታይምስ የተሰኘዉ የአማርኛ ጋዜጣ አዘጋጅ ዳዊት ከበደ CPJ-በሚል የእንግሊዝኛ ምሕፃረ-ቃል የሚጠራዉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ተቋም የሰጠዉን ሽልማት ዛሬ ማታ ኒዮርክ-ዩናይትድ ስቴትስ ዉስጥ በሚከናወን ሥነ-ሥርዓት ይረከባል።CPJ እንዳስታወቀዉ ጋዜጠኛ ዳዊት ለዘንድሮዉ የአለም የፕረስ ነፃነት ሽልማት የበቃዉ የሚደርስበትን ፖለቲካዊ ጫናና ወከባ ተቋቋሞ ፖለቲካዊ መረጃን ለሕዝብ በማቅረቡ ነዉ።የዋሽንግተኑ ወኪላችን አበበ ፈለቀ እንደዘገበዉ CPJ የዘንድሮዉን ሽልማቱን ከዳዊት በተጨማሪ ለሰወስት የሌሎች ሐገራት ጋዜጠኞችም ይሰጣል።
አበበ ፈለቀ
ነጋሽ መሐመድ