1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የፕሬዚዳንት አልሲሲ የሰሞኑ ዛቻና አንድምታው

ሐሙስ፣ መጋቢት 23 2013

የግብፅ ፕሬዝዳንት አብዱል ፈታህ አል ሲሲ የግብፅ ጠብታ ውኃ ከተነካ አካባቢው ቀውስ ያስተናግዳል ሲሉ የመንግስታቸውን አቋም አንፀባርቀዋል። ይህ የግብፅ አቋም አንድም የማስፈራራት ፣ በሌላ በኩል ከውኃ ሙሌቱ በፊት በኢትዮጵያ ላይ ጫና የማሳደር ዓላማ ያለው መሆኑን ያነጋገርናቸው ሁለት የዘርፉ አዋቂዎች ተናግረዋል።

https://p.dw.com/p/3rUAS
Ägypten Handball WM 2021 Eröffnung
ምስል Mohamed Abd El Ghany/AFP/Getty Images

የግብጹ ፕሬዚዳንት ንግግር ምን አንድምታ አለው?

ኢትዮጵያ በመጪው ክረምት የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዙር የውኃ ሙሌት እንደምታከናውን መንግሥት አሳውቋል። ይህንን ተከትሎ የግብፅ ፕሬዝዳንት አብዱል ፈታህ አል ሲሲ «የግብፅ ጠብታ ውኃ ከተነካ አካባቢው ቀውስ ያስተናግዳል» ሲሉ የመንግሥታቸውን አቋም አንፀባርቀዋል። ይህ የግብፅ አቋም አንድም የማስፈራራት ፣ በሌላ በኩል ከውኃ ሙሌቱ በፊት በኢትዮጵያ ላይ ጫና የማሳደር ዓላማ ያለው መሆኑን ያነጋገርናቸው ሁለት የዘርፉ አዋቂዎች ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በውስጥ አንድነቷ ፀንታ ሥራዋን መቀጠልና የሚመጣን ጫና መቋቋም ይገባልም ብለዋል ባለሙያዎቹ። በኢትዮጵያ ሱዳንና ግብፅ መካከል ሲደረግ የቆየው የረጅም ጊዜ ድርድር ከተቋረጠ ሰነባብቷል። የኢትዮጵያን ድንበር ጥሳ በመግባት ወረራ መፈፀሟ የተነገረው ሱዳንም ከግብፅ ጋር ወታደራዊ ልምምድ በማድረግ ድርድሩ እንዲጓተት እያደረገች መሆኑን የኢትዮጵያ መንግሥት ገልጿል። የኢትዮጵያ መንግሥት የግብፅ ፕሬዚዳንት ንግግር ላይ ግን እስካሁን ያለው ነገር የለም።

ሰለሞን ሙጬ
ታምራት ዲንሳ
ሸዋዬ ለገሠ