የፊልም ፕሮዲውሰር እና ዳሬክተር -ቅድስት ባየልኝ
ሰኞ፣ ጥር 7 2004ማስታወቂያ
ቅድስት ባየልኝ እስካሁን ሶስት ፊልሞችን ሰርታ ለዕይታ አቅርባለች። አሁንም የመጨረሻ ፊልሟን ለማስተዋወቅ በኢትዮጵያ ትገኛለች። ቅድስት ስለምትሰራቸው ፊልሞች ብቻ ሳይሆን ስለሷ የህይወት ታሪክ መለስ ብላ ታስታውሰናለች።
ቅድስት ባየልኝ ያጠናችው የስነ ልቦና ትምህርት ነው። ሙያዋ ግን ፤ የፊልም ፕሮዲውሰር እና አዘጋጅ። አንድ የፊልም አዘጋጅ ስላለበት ኃላፊነት እና ስራ፤ ከፊልም አቀናባሪዎች፣ ከፊልም ቀረፃ ባለሙያዎች እና ተዋናዮች ጋ ፣ቅስድት ምን አይነት ቅርበት እንዳላት እንዲሁም ለሌሎችም ጥያቄዎች መልስ ሰታናለች።
የወጣት ልጆችን ፈተና በተለይም በውጭው አገር ያለውን ፈተና ለማንፀባረቅ ስለጣረችበት -«ከአትላንቲክ ባሻገር» ፊልም ፤ የበለጠ ማወቅ ከፈለጉ ዝርዝሩን ከዛሬው የወጣቶች ክፍለ ጊዜ ያገኙታል።
ልደት አበበ