የግብፁ ፕሬዝዳት መልዕክት
ሐሙስ፣ መስከረም 17 2005ማስታወቂያ
አፍሪቃዉያን ችግሮቻቸዉን ለማስወገድ የሚያደርጉትን ጥረት የበለፀገዉ ዓለም የመርዳት ሐላፊነት እንዳለበት አዲሱ የግብፅ ፕሬዝዳት መሐመድ ሙርሲ አስታወቁ።ከግብፁ ሕዝባዊ አብዮት በሕዋላ በተደረገዉ ምርጫ ሥልጣን የያዙት ሙርሲይ ኒዮርክ ለተሰየመዉ ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ባደረጉት ንግግር እንዳሉት የበለፀጉት ሐገራት የአፍሪቃ አምባገነን ገዢዎችን መደገፋቸዉን አቁመዉ የሕዝቡን ችግር ለማቃለል ለሚጥሩት ወገኖች ተገቢዉን ድጋፍ ማድረግ አለባቸዉ።ሙርሲይ አክለዉ እንዳሉት ሐገራቸዉ ፍልስጤሞች የራሳቸዉ መንግሥት ለማቆም፥ አፍሪቃዉያን ለዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ የሚያደርጉትን ትግል ትደግፋለች።የዋሽግተን ዲሲ ዘጋቢያችን አበበ ፈለቀ ዝር ዝር ዘገባ ልኮልናል።
አበበ ፈለቀ
ነጋሽ መሐመድ
ሸዋዬ ለገሠ