የጀርመን ያገለገሉ መኪናዎች
ረቡዕ፣ ነሐሴ 6 2001ማስታወቂያ
በዚሁ መሠረትም በአፍሪቃ ብቻ ሳይሆን በምሥራቅ አዉሮጳ አንዳንድ ሀገራት ሳይቀር በአዲስነት ተገዝተዉ ጎዳናዉን ሊያጣብቡ የሚችሉትን አዉቶሞቢሎች ባለቤቶቻቸዉ ለዚህ ለሚጨፈልቀዉ ድርጅት እየሰጡ ገንዘብ ተቀብለዋል። መኪናዎቹ እጅግ ዘመናዊ የሚባሉ፤ ዉድ፤ ለተለያየ ጉዳይ የሚጠቅሙ ኤሌክትሮኒክሶች የተገጠሙላቸዉ፤ 50,000 ግፋ ቢል ከ100,000 ኪሎ ሜትር በላይ ያልተጓዙ መሆናቸዉንም ከጀርመን ያገለገሉ መኪናዎችን እየገዙ ወደአፍሪቃ የሚልኩት ነጋዴዎች ይገልጻሉ። ይህ ዜና እንደተሰማና ተግባሩም እንደተጀመረ ወደአፍሪቃ ሰልባጅ መኪና የሚልኩት ነጋዴዎች ቅሬታ ብቻ ሳይሆን ድንጋጤም ገጥሟቸዋል። ሰሞኑን የተሰማዉ ደግሞ ሌላ ታሪክ ነዉ። ሊጨፈለቁ እየተፈረደባቸዉ ገንዘብ የተበላባቸዉ አዉቶሞቢሎች ወደአፍሪቃ ገብተዋል።
ይልማ ኃይለሚካኤል/ሸዋዬ ለገሠ