የዶ/ር ፍቅሩ ማሩ አቤቱታ
ማክሰኞ፣ ሰኔ 9 2007ማስታወቂያ
ኢትዮጵያ ዉስጥ በሙስና ጥርጣሬ የታሠሩት ኢትዮጵያዊ ሲዊድናዊዉ የልብ ቀዶ ሕክምና አዋቂ ዶ/ር ፍቅሩ ማሩ ከእስር ቤት እንዲፈቱ የሲዊድን መንግሥት ግፊት ያደርግ ዘንድ ጠየቁ።ዶክተር ፍቅሩ ለሲዊድን ጠቅላይ ሚንስትርና ዉጪ ጉዳይ ሚንስትር በጻፉት ተመሳሳይ ደብዳቤ የኢትዮጵያ የፍትሕ ሥርዓት እስከፊ በመሆኑ የሲዊድን መንግሥት የዜጋዉን መብት ለማስከበር አስፈላጊዉን ጥረት ማድረግ አለበት።ዶክተሩ በደብዳቤያቸዉ እንደገለጹት የሲዊድን መንግሥት የዜጋዉን መብት ለማስከበር ይሕን ያሕል ጊዜ መፍጀት አልነበረበትም።ዶክተር ፍቅሩ ከታሠሩ ሁለት ዓመታቸዉ ነዉ።የስቶክሆልሙ ወኪላችን ቴዎድሮስ ምሕረቱ ዝርዝር ዘገባ ልኮልናል።
ቴዎድሮስ ምሕረቱ
ነጋሽ መሐመድ
አርያም ተክሌ