1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የዶይቼ ቬለ አመራሮች ጉብኝት በጎንደር

እሑድ፣ መጋቢት 15 2011

የDW ከፍተኛ አመራሮች ልዑካን ቡድን በዛሬው ዕለት በጎንደር ከተማ ጉብኝት አድርገዋል። ከልዑካኑ መካከል የDW ዋና ሥራ አስፈፃሚ ፒተር ሉምቡርግ፣ የአፍሪካ ክፍል ተጠሪ ክላውስ ሽቴከር እና የአማርኛዉ ክፍል ተጠሪ ሉድገር ሻዶምስኪ ይገኙበታል።

https://p.dw.com/p/3FamY
Äthiopien Gonder Besuch DW-Delegation
ምስል DW/Y. Gebregziabher

የዶይቼ ቬለ አመራሮች ጉብኝት በጎንደር

የDW ከፍተኛ አመራሮች ልዑካን ቡድን በዛሬው ዕለት በጎንደር ከተማ ጉብኝት አድርገዋል። ከልዑካኑ መካከል የDW ዋና ሥራ አስፈፃሚ ፒተር ሉምቡርግ፣ የአፍሪካ ክፍል ተጠሪ ክላውስ ሽቴከር እና የአማርኛዉ ክፍል ተጠሪ ሉድገር ሻዶምስኪ ይገኙበታል።

በጉብኝቱ በጎንደር ከተማ የደብረ ብርሀን ስላሴ ቤተ-ክርስቲያን፣ በከተማዋ የሚገኙ አብያተ-መንግሥታት እና በአካባቢው የሚገኙ ታሪካዊ ቦታዎችን ተመልክተዋል።   

በጎንደር ከተማ ቆይታቸው ከፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች፤ የማኅበረሰብ ወኪሎች፤ የሀገር ሽማግሌዎችን ጨምሮ የተለያዩ ሰዎች በተገኙበት ውይይት ማድረጋቸውን በቦታው የተገኘው ዮሐንስ ገብረእግዚዓብሔር ዘግቧል።  

በውይይታቸው የኢትዮጵያ ነባራዊ ፖለቲን ጨምሮ የተለያዩ ርዕሰ-ጉዳዮች ተነስተዋል።

ዮሐንስ ገብረእግዚአብሔር

እሸቴ በቀለ