የዶክተር ዐቢይ የአንድ ዓመት አስተዳደር
ረቡዕ፣ ሚያዝያ 2 2011ማስታወቂያ
ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት ሂዩመን ራይትስ ዋች በኢትዮጵያ ባለፈው አንድ ዓመት ልዩ ልዩ መብቶች እየተከበሩ ቢሆንም የለውጡ ቀጣይነት ግን እንደሚያሳስበው አስታወቀ።ድርጅቱ ካለፈው ሳምንት አንስቶ በ8 ርዕሶች በተከታታይ ባወጣው ዘገባ በኢትዮጵያ የመናገር፣ የመጻፍ፣ የመሰብሰብ፣ የመደራጀት እና ሌሎች መሰል መብቶች እየተከበሩ መሆኑን ገልጿል። ይሁን እና በድርጅቱ የኢትዮጵያ እና የኤርትራ የሰብዓዊ መብት ይዞታ ከፍተኛ ተመራማሪ ፌሊክስ ሆርን በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች በተባባሰው ግጭት ምክንያት የለውጡ ቀጣይነት እንደሚያሳስብ ተናግረዋል። መንግሥት ግልጽ እቅድ በማውጣትም ህግ እና ስርዓትን ሊያስከብር እንደሚገባም አሳስበዋል። ያነጋገራቸው ወኪላችን መክብብ ሸዋ ዝርዝሩን አዘጋጅቷል።
መክብብ ሸዋ
ኂሩት መለሰ
ነጋሽ መሐመድ