ዶናልድ ትራምፕ
ዓርብ፣ ሐምሌ 15 2008ማስታወቂያ
41ኛው የአሜሪካን የሪፐብሊካን ፓርቲ ጉባኤ፣ ፓርቲውን ወክለው በእጩ ፕሬዝዳንትነት እንዲወዳደሩ የመረጣቸው ዶናልድ ትራምፕ ትናንት በፓርቲያቸው ጉባኤ ላይ ባሰሙት ንግግር፣ ሃገሪቷ የምትዋዥቅባቸውን ልዩ ልዩ ችግሮች ብቻቸውን ማስወገድ እንደሚችሉ አስታወቁ ። ትራፕም በእጩነት ከተሰየሙ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ባሰሙት 75 ደቂቃ በወሰደ ንግግራቸው የአሜሪካንን ደህንነት እንደገና ለማስጠበቅ ፣ ወደ አሜሪካ የሚደረግ ህገ ወጥ ስደትን ለማስቆም እና አሜሪካንን ታላቅ ለማድረግ ቃል ገብተዋል ። አወዛጋቢው የ70 ዓመቱ ባለፀጋ ትራምፕ የኢንድያና ክፍለ ግዛት ሀገረ ገዥ ማይክ ፔንሰንን በምክትል እጩ ፕሬዝዳንትነት መርጠዋል ። የ45 ተኛው የአሜሪካን ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ እጩ ተፎካካሪ ምርጫ ላይ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ተቃዋሚዎችም ተገኝተዋል ። መክብብ ሸዋ ከዋሽንግተን ዲሲ ዝርዝር አለው ።
መክብብ ሸዋ
ኂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ