የድሬዳዋ ፖሊስ ሥልጠና
ዓርብ፣ ሚያዝያ 18 2011ማስታወቂያ
የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር በከተማይቱ የሚገኙ ፖሊሶችን በሙሉ ዳግም ሊያሰለጥን ማቀዱን አስታወቀ።የመስተዳድሩ ፖሊስ አባላት ኃላፊነታቸዉን በአግባቡ አይወጡም የሚል ወቀሳና ትችት በተደጋጋሚ ይሰነዘርባቸዋል።የከተማይቱ ፖሊስ ኮሚሽን እንደሚለዉ «ተሐድሶ» የተባለዉ ሥልጠና በፖሊሶች ሥራ፣አሰራርና ሥርዓት ላይ የሚነሱ ቅሬታዎችን ለማቃለል ይረዳል።ሥልጠናዉ ከአንድ ወር እስከ አንድ ወር ተኩል ይፈጃል ነዉ የተባለዉ።ሥልጠናዉ የሚጀመርበት ጊዜና ሥፍራ ግን በግልፅ አልተነገረም።
መሳይ ተክሉ
ነጋሽ መሐመድ
ተስፋለም ወልደየስ