1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንታዊ ክርክር

ማክሰኞ፣ ጥቅምት 13 2005

በአብዛኛዉ በዩናይትድ ስቴትስ የዉጪ መርሕ ላይ ባተኮረዉ ክርክር ፕሬዝዳት ኦባማ የአራት አመት የመሪነት ልምዳቸዉን በትክክል ማንፀባረቅ መቻላቸዉን ክርክሩን የተከታተሉ ታዛቢዎች አረጋግጠዉላቸዋል።

https://p.dw.com/p/16V6B
Republican presidential candidate, former Massachusetts Gov. Mitt Romney and President Barack Obama walks past each other on stage at the end of the last debate at Lynn University, Monday, Oct. 22, 2012, in Boca Raton, Fla. (Foto:Pablo Martinez Monsivais/AP/dapd)
ኦባማና ሮምኒምስል AP

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንታዊ ዕጩዎች ትናንት ማታ ባደረጉት ሰወስተኛና የመጨረሻ የፊት ለፊት ክርክር በሥልጣን ላይ ያሉት ፕሬዝዳት ባራክ ኦባማ የሪፐብሊካን ተቀናቃኛቸዉን ሚት ሮምኒን በሰፊ ልዩነት ማሸነፋቸዉ ተመሠከረ።በአብዛኛዉ በዩናይትድ ስቴትስ የዉጪ መርሕ ላይ ባተኮረዉ ክርክር ፕሬዝዳት ኦባማ የአራት አመት የመሪነት ልምዳቸዉን በትክክል ማንፀባረቅ መቻላቸዉን ክርክሩን የተከታተሉ ታዛቢዎች አረጋግጠዉላቸዋል።አገረ-ገዢ ሚት ሮምኒ በበኩላቸዉ ወትሮ ከነበራቸዉ የቀኝ አክራሪ አቋም ተለሳልሰዉ ባንዳድ ጉዳዮች የኦባማ መስተዳድርን መርሕ እስከ መደገፍ ደርሰዋል።የዋሽግተን ዲሲዉ ወኪላችን አበበ ፈለቀ ዝር ዝር ዘገባ አለዉ።

አበበ ፈለቀ

ነጋሽ መሐመድ

ሸዋዬ ለገሰ