የዓለም ዓቀፍ ለኢትዮጵያውያን ትብብር ልገሳ
ዓርብ፣ ታኅሣሥ 25 2006ማስታወቂያ
በሳውዲ አረቢያ ስቃይና እንግልት የደረሰባቸውን ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ለመታደግ የተቋቋመው ዓለም ዓቀፍ ትብብር የመጀመሪያ የገንዘብ ድጋፍ ለዓለም ዓቀፉ የስደተኞች መርጃ ተቋም በእንግሊዘኛው ምህፃር IOM ዛሬ አስረከበ ። የትብብሩ ሊቀመንበር አርቲስት ታማኝ በየነ ማህበሩ የጀመረው የገንዘብ ድጋፍ የማሰባሰብ እንቅስቃሴ በተቀናጀ መልኩ እንደሚቀጥል አስታውቋል ። በመላው ዓለም የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የበኩላቸውን ድጋፍ እንዲያደርጉም ጥሪ አቅርቧል ። የገንዘብ ድጋፉን የተረከበው የዓለም ዓቀፉ የስደተኞች መርጃ ተቋም የውጭ ግንኙነት ሃላፊ በበኩላቸው ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን የማቋቋሙን ተግባር ለመቀጠል መጠነ ሰፊ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው ጠቁመዋል ።
አበበ ፈለቀ
ኂሩት መለሰ
ተክሌ የኋላ