የወለኔ ፓርቲ መሪዎች ተለቀቁ
ረቡዕ፣ ኅዳር 18 2006ማስታወቂያ
የወለኔ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ መሪዎች ከዓንድ ዓመት በላይ ከታሰሩ በሕዋላ ሰሞኑን በነፃ ተለቅቀዋል።የፓርቲዉ መሪዎች ከእስር ከተፈቱ በሕዋላ አዲስ አበባ እንዳሳታወቁት ካአንድ ዓመት በላይ ለእስራት የተዳረጉት በኢትዮጵያ ሕገ-መንግሥት የተረጋገጠዉ የወለኔ ሕዝብ ማንነትና መብት እንዲከበር በመጠየቃቸዉ ነዉ።ተመሳሳይ ጥያቄ ያነሱ ሌሎች የፓርቲዉ ባለሥልጣናት አሁንም እንደታሠሩ መሆናቸዉን አስታዉቀዋል።የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ጌታቸዉ ተድላ ሐይለ ጊዮርጊስ ያነጋገራቸዉ የፓርቲዉ ምክትል ሊቀመንበር እንዳስታወቁት የሕዝባቸዉ መብት እንዲከበር የጀመሩትን ትግል ከእንግዲሕም ይቀጥላሉ።
ጌታቸዉ ተድላ ሐይለ ጊዮርጊስ
ነጋሽ መሐመድ
ሒሩት መለሰ