1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኦባማ ጋዜጣዊ መግለጫ

ሐሙስ፣ ኅዳር 6 2005

ኦባማ በጋዜጣዊ መግለጫቸው ለሃብታም አሜሪካውያን ያቀዱትን የግብር ጭማሪ ሃገሪቱን ከኤኮኖሚ ውድቀት ለማዳን ሲሉ ሪፐብሊካውያን መቀበል እንዳለባቸውም አሳስበዋል ። ከአጠቃላዩ ህዝብ 2 በመቶ በሚሆኑት አሜሪካውያን የግብር ጭማሪ መደረጉን ሪፐብሊካውያን ይቃወማሉ ።

https://p.dw.com/p/16jyT
U.S. President Barack Obama gestures while addressing his first news conference since his reelection, at the White House in Washington November 14, 2012. REUTERS/Kevin Lamarque (UNITED STATES - Tags: POLITICS)
ምስል Reuters


የአሜሪካን ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማ ሪፐብሊካውያን እንደሚፈልጉት ለባለሃብቶች የግብር ፋታ እንደማይሰጡ ዳግም አስታወቁ ። ኦባማ ለ 2 ተኛ የሥልጣን ዘመን ከተመረጡ በኋላ ትናንት ለመጀመሪያ ጊዜ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ለሃብታም አሜሪካውያን ያቀዱትን የግብር ጭማሪ ሃገሪቱን ከኤኮኖሚ ውድቀት ለማዳን ሲሉ ሪፐብሊካውያን መቀበል እንዳለባቸውም አሳስበዋል ። ከአጠቃላዩ ህዝብ 2 በመቶ በሚሆኑት አሜሪካውያን የግብር ጭማሪ መደረጉን ሪፐብሊካውያን ይቃወማሉ ። ኦባማ በትናንቱ ጋዜጣዊ መግለጫቸው በኢኮኖሚ በውጭ ግንኙነት በስደተኞችና በሌሎች ጉዳዮች ላይ ለተነሱ ጥያቄዎችም መልስ ሰጥተዋል ። የዋሽንግተን ዲሲው ዘጋቢያችን አበበ ፈለቀ ዝርዝሩን ልኮልናል ።
አበበ ፈለቀ
ሂሩት መለሰ
ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ