የኦሮሞ የፖለቲካ ፓርቲዎች አቤቱታ
ማክሰኞ፣ የካቲት 24 2007ማስታወቂያ
ፓርቲዎቹ ከዚህ ቀደም ከተደረሰበት ስምምነት ውጭ አባላቶቻቸው እንደሚንገላቱ የበጀት ድጎማ እንደማይሰጣቸውና ለምርጫ ቅስቀሳ አመቺ የአየር ጊዜ እንደተነፈጉ ተናግረዋል ። ዶቼቬለ ያነጋገራቸው የምርጫ ቦርድ ሃላፊ ግን ያልተፈታ ችግር እንደሌለ ተናግረዋል። በጀትን በተመለከተ ለተወዳዳሪ ፓርቲዎች በሙሉ በእኩል የሚካፈፈለው ገንዘብ ሰሞኑን እንደሚለቀቅ አስታውቀዋል ።ሁለቱንም ወገኖች ያነጋገረው የአዲስ አበባው ወኪላችን ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ ዝርዝሩን ልኮልናል ።